Service Times: Sundays 10 am - 1 pm

የወንጌል ሥርጭት

በጥናትና በስልት በተደገፈ መንገድ ልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ወንጌል በመስማት እንዲድኑ ምቹ ሁኔታ ፈጥሮ መልእክቱ እያደረሰ ወይም እንዲደርስ እያደረገ ይገኛል፡፡ ይህንንም ከባቢያዊና ራቅ ባሉት መካከል ሚዛን በጠበቀ መንገድ ለማድረግ ይተጋል። በተጨማሪም የወንጌል አዋጁ ያስገኛቸውን አዲስ አማንያን እንክብካቤ የሚያገኙበት ሥርዓት ዘርግቶ ተገቢውን የክትትል ትምህርት እያገኙ የሚያድጉበትን መንገድ አመቻችቶ በመሥራት ላይ ነው። በየጊዜውም ለልዩ ልዩ ተልእኮ ፈጥነው የሚደርሱ ግብረ ኃይል ያደራጃል። ወንጌልን ልዩ ልዩ ስልቶችን (ድራማ፣ስነጽሁፍ፣ ፊልም ወዘተ…) በመጠቀም እንዲተላለፍ ሲያደርግ ቆይቷል እያደረገም ይገኛል፡፡ወንጌልን ከማድረስ አኳያ ልዩ ልዩ ስልጠናዎችና አውደጥናቶች እንዲሰጡ በማድረግ ለወንጌል ሥርጭት መተግበር የበኩሉን ለመወጣት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። አውራ የተልእኮውም ትኩረት «የማዳኑ ወንጌል ያለማቋረጥ በማወጅ፣ ኃጢአተኛውን ለንስሐ እናዘጋጅ» የሚል ነው።