Service Times: Sundays 10 am - 1 pm

ትምህርትና ሥልጠና

በመጽሐፍ ቅዱስ እይታ የሚመራ፣ ወቅታዊ ጥያቄዎችን መላሽ የሆነ አስተምህሮን በሁነኛ ግብ ቀርጸን ክርስቶስ ተኮር ሕይወት እንዲሰርጽ የበኩሉን ይወጣል። ተዛማጅ የሆኑ አውደ ጥናቶችና፣ ሲምፓዚየሞች፣ እንዲሁም ትምህርቶች እንዲዘጋጁ ያደርጋል፤ ለአድማጮችም ሆነ ለተሳታፊዎች የሚቀርቡበትን ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፤ አወዘጋቢ ጉዳዮች ሲነሱ ውዝግቡ ብስለት በተሞላበት መንገድ እንዲያዝ ርዕሰ ጉዳዮቹ በስፋት የሚታዩበት በጥልቀት የሚተነተኑበትና አቋም የሚያዝበት ሁኔታ ላይ እንዲደርስ ጥረት ያደርጋል፣ ጥልቀት ያላቸው ጥናታዊ ጽሁፎች ለወንጌል ያላቸውን ጠቀሜታ ይቃኛል፣ ለምእመናን መታነጽ የሚወሉበትን መንገድ ይቀይሳል።