Service Times: Sundays 10 am - 1 pm

የወጣት ጎልማሶች አገልግሎት

ቃሉን ማእከል ያደረገ፣ ስሜታቸውን ያገናዘበ አገልግሎት የሚሠርጽበትን መንገድ ያመቻቻል፤ ተግባራዊነቱንም ይከታተላል፤ወጣት ጎልማሶች ኃላፊነት የሚሰማቸው ባለአደራዎች እንዲሆኑ ብቃት የሚያጎለብቱብን መንገድ ይቀይሳል። ወጣቶች በእምነታቸው ሳያመዛዝኑ የተቀበሉት ብቻ ሳይሆን የራሳቸው እንደ ቃሉ የሆነ አቋም እንዲኖራቸው ተገቢውን ትጥቅ ያቀብላል። ከስሜትና ከግልብ መረዳት ጽዱ የሆነ፣ የሰከነ መንፈሳዊ አቋም የእነርሱነታቸው መገለጫ እንዲሆን ተገቢውን ሁኔታ ያመቻቻል፣ ለዚያም ግብ ይሠራል፡፡ ወጣት ጎልማሶች ከቡድናዊ ግፊትና ከጅምላ አቋም ይልቅ የጌታን ፈቃድ ለግላቸው ፈልገው ማወቅ ለሚችሉበት ሁኔታ አቅጣጫን ይቀይሳል፣ ለተግባራዊነቱም ጠንክሮ ይሠራል። ወጣት ጎልማሶች ከቤተሰብ፣ ከእድሜ እኩዮቻቸው፣ ከቤተ ክርስቲያንና ከሚኖሩበት ማኅበረሰብ ጋር በትብብር በመሥራት ተፈላጊው ለውጥ በአካባቢው እንዲመጣ በቅንጅት የሚሠሩበትን ሁኔታ ያመቻቻል፣ በመደበኛው የቤተ ክርስቲያን ፕሮግራሞች በማኅበረሰቡ ሕይወት እንዲሳተፉ ሁኔታዎችን ያመቻቻል። ለትውልድ ክፈተት ድልድይ በማበጀት ወጣቱ ጎልማሶች እንደ ተቀባይ አቀባይ መንፈሳዊ ተልእኮውን እንዲወጣ ወጣቶችን ለተልእኮ ያበረታታል፣ ለተግባራዊነቱም ይሠራል፡፡ በመሆኑም ቃሉን የሚሰጠውን ጽዳት በመቀበል፣ ለክርስቶስ በሁለንተና የተገዛ ሕይወት በመኖር ተልእኮን ከግቡ ያደርሳል።