Service Times: Sundays 10 am - 1 pm

የፀሎት አገልግሎት

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጸሎት በምእመናን ሕይወትና ልምምድ እንዲሠርጽ ተገቢውን እርምጃ ይወስዳል፣ የወቅቱን የጸሎት ርዕሰ ጉዳዮች በመቅረጽ የጸሎት ሠራዊት በምልጃ እንዲሳተፉ ያነሳሳል። የኅብር ጸሎት ባሕል እንዲዳብር ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ማላጆች የሚበራከቱበትን መንገድ እየቀየሰ ምእመናንን በሙሉ ለጸሎት ለማነሳሳት የበኩሉን ይወጣል። ለሕመምተኞች የሚጸለይበትን ቀጣይ የፈውስ አገልግሎት የሚደራጅበትን ሁኔታ ይቀይሳል ተግባራዊነቱን ይከታተላል፤ዘወትር እሁድ ከአምልኮ በኋላ የጸሎት እርዳታ የሚሹ ምእመናን እንክብካቤ እንዲያገኙ አገልጋዮችን ያነሳሳል። ከመንፈስ ቅዱስ በመነጨ ምሪት፣ በሁሉን ቻይ ጌታ ፊት በመውደቅ ምላሻችንን ተቀብለን እርሱን ለማክበር መትጋትን የአገልግሎቱ መታያ አድርጎ ይንቀሳቀሳል።