Service Times: Sundays 10 am - 1 pm

(የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት)

የቤት ኅብረት አገልግሎት

ቃሉን ተገቢውን የአተረጓጎም ስልት በመከተል በማጥናት፣ ትክክለኛ ፍቺ እየሰጡ ከሕይወት ጋር በማዋሃድ፣ ተልእኮን ይወጣል። የዝርዝር መጽሐፍ ቅዱስ አጠናን ዘዴን (Inductive Bible study) በመተግበር መጽሐፍ ቅዱስ በትንንሽ የቤት ሕብረቶች እንዲጠና ምቹ ሁኔታ ፈጥሮ ምእመናን እንዲተናነጹ እያደረገም ይገኛል። ምእመናን ጸጋቸውን የሚለዩበት እድል እንዲያገኙ የተማሩበትን የሚያካፍሉበት መስመር እያመቻቸ ያሳድጋል። መጽሐፍ ቅዱስ ሚዛናዊ በሆኑ ርእሰ ጉዳዮች እየተጠና ምእመናን የተመጣጠነ መንፈሳዊ ምግብ እንዲያገኙ ያለሰለሰ ጥረት ያደርጋል። በየወቅቱ የሚጠኑበት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችን እየመረጠ ጥናቱ እንዲሰናዳና እንዲተገበር ከማድረጉ ባሻገር፣ በተቻለ መጠን አንድ ወጥ ሆነው በየጥናት ቡድኑ እንዲያልቁ እያመቻቸ ሥራውን ይሠራል።