Service Times: Sundays 10 am - 1 pm

(ጉብኝትና ማማከር)

የእንክብካቤ አገልግሎት

በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉት አባላት እርስበርስ እንዲተዋወቁና እንዲደጋፉ በግንኙነት መረብ አስተሳስሮ ተልእኮ ይወጣል። ምእምናን ባሉበት ሥፍራዎች ሁሉ አዳዲስ የቤት ኅብረቶችን እንዲደራጁ ጉብኝቱ እንዲቀላጠፍ ያደርጋል። የሚጎበኙ ምእመናን ቅደም ተከተል ለማስያዝ አስቀድሞ ተጎብኚዎችን ነጥሎ የማውጣቱን ሥራ በትኩረት ይሠራል:: ለሚጎበኙ ግለሰቦች ሁኔታ የሚመቹ ጎብኚዎችን በጥንቃቄ በመምረጥ ጎብኚና ተጎብኚን የማስተሳሰሩን ሥራ እያቀላጠፈ ለጉብኝት አመቺ ስልት እየነደፈ በተግባር ላይ ማዋል ቀዳሚ የተልእኮው አካል ነው። በተጨማሪም ጎብኚዎች በግል መነሳሳት ሳይሆን ከቤተ ክርስቲያን ተመድበው የሚንቀሳቀሱበትን ሁኔታ እያመቻቸ ምእመናን ወቅቱን ያገናዘበ እገዛ እንዲቀበሉ ሁኔታዎችን እያመቻቸ ተልእኮውን ይወጣል። የማማከሩንም ሥራ ከአገልግሎት ቢሮው ጋር በመቀናጀት ለመፈጸም የበኩሉን ይወጣል። የነርሶችን አገልግሎትም በመጠቀም ምእመናን ጤና ነክ እንክብካቤ እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። በመሆኑም «በክርስቶስ ፍቅር ተንቀሳቅሰን፣ ለተቸገሩ ደርሰን፣ የተረሳን አስታውሰን የርህርሄ እንክብካቤ እንሰጣለን፡፡» የሚለውን መርህ ለመተግበር ይሠራል።