Service Times: Sundays 10 am - 1 pm

የዝማሬ አገልግሎት

መጽሐፍ ቅዱስ በብሉይ ኪዳንም ሆነ በአዲስ ኪዳን ደጋግሞ የሚያስተዋወቅን የእግዚአብሔር ሕዝብ የሚዘምር ሕዝብ መሆኑን ነው፡፡ ዝማሬም አምላክና ሰው ያስተሳሰረ ድንቅ የመለኮት ሥራ መሆኑን በተደጋጋሚ ያበሥራል፡፡ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዝማሬ ትኩረቱን እግዚአብሔር ላይ ያደረገ፣ ከእርሱ የሚመነጭ፣ የእርሱን ረቂቅ ሥራ ገላጭና እርሱ በመረጠው ሁኔታ ፍጡርንና ፈጣሪን የሚያሳትፍ የአምላክ ሥራ ነው፡፡ በመሆኑም የቤተክርስቲያናችን የዝማሬ አገልግሎት በማራኪ ሙዚቃዊ ቅንብር የተደራጀ፣ ለባሕላዊ እሴቶቻችን እውቅና የሰጠ እንዲሁም ክርስቶስን ማዕከል ያደረገ አምልኮን የሕይወት ዘይቤ ያደረገ ዝማሬ አገልግሎት ለመስጠት ያለሰለሰ ጥረት ያደርጋል።