Service Times: Sundays 10 am - 1 pm

የሚዲያ አገልግሎት

የቤተክርስቲያኒቱን ውሳጣዊና ውጫዊ ግንኙነት ውጤታማ ለማደረግ የዘመነ የኮምኒኬሽን አገልግሎት እንዲጎለብት በትጋት እየሠራ ይገኛል። በቀደሙት ዘመናት በቴፕ፣ በሲዲ፣ በቪሲዲ፣ በዲቪድ የመነቃቂያ ፕሮግራሞች ላይ የተቀዱትንም ሆነ በመደበኛ ፕሮግራም ላይ የተቀዱትን ፕሮግራሙ ላመለጣቸው ምእመናን ተባዝተው ቀለል ባለ ዋጋ እንዲደርሳቸው በማድረግ አገልግሎቱን ሲያበረክት ቆይቷል። በየወቅቱ ዜና ቤተክርስቲያንንም ሆነ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ትንተና የሚሰጡ የኅትመት ሥራዎች እንዲሠራጩ የበኩሉ ሲፈጽም ቆይቷል። በውስጡም የኦዲዮቪዥዋል፣ የቪዲዮ፣ የድምፅ፣ የበይነ መረብ፣ የቴፕ፣ የኅትመት፣ የትርጉም አገልግሎቶችን በማደራጀት አገልግሎቱ ተደራሽ እንዲሆን ያለሰለሰ ጥረት አድርጓል። ሳምንታዊው መደበኛ አገልግሎት በኢንተርኔት በቅርብና በሩቅ ላሉት በቀጥታ ሥርጭት እንዲደርሳቸው እያደረገ ኃላፊነቱን በመወጣት ላይ ነው። በመሆኑም ለአያሌ ዓመታት የሚመራበት መርህ «በህብር እንቅስቃሴያችን ፍቅሩን ማስተጋባት ነው ግባችን፡፡ የየፊና ደርሻችንን ተወጥተን መልእክታችንን ለተቀባዮቹ እናደርሳለን፡፡» የሚል ነው።