Service Times: Sundays 10 am - 1 pm

የቃሉ አገልግሎት

‹‹ቃሉን ግልጽ፣ ትክክልና የጠራ አድርጎ በማቅረብ ለሕይወት ለዋጭ ግብ መሥራት›› ነው። ይህንንም የሚያደርገው ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ (ብሉይ ኪዳንና አዲስ ኪዳን) በትምህርትና በስብከት እንዲዳሰስ ተግባራዊ እርምጃ በመውሰድ ነው። ይህንንም ተዛማጅ የሆኑ ተግባራዊና ታሪካዊ እውነቶች ለምእመኑ እንዲቀርቡ በማድረግ ይፈጽማል።ቃሉ ክህነታዊና ነቢያዊ ሚዛንን በጠበቀ ሁኔታ አማኞችን እንዲያገኛቸው ሁኔታዎችን ያመቻቻል። ቤተክርስቲያን የምትጠራና የምታንጽ እንድትሆን በቃሉ ውስጥ የድነት መልእክት እንዲጠቃለልና የወንጌል ጥሪ ሆን ተብሎ እንዲደረግም ተገቢውን እርምጃ ይወስዳል። መጽሐፍ ቅዱስ በሥላሴያዊ እይታ እንዲነበብና ቤተ ክርስቲያንም የሥላሴ ማኅበርተኛ መሆኗን ለሚያሳውቅና ለሚያለማምድ መንፈሳዊ እሴት እየሠራ ተልእኮውን ይወጣል። ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮዎች ጊዚያቸውን ጠብቀው ለምእመኑ መቅረባቸውን እየተከታተለና ድግግሞሽ እንዳይኖር ተገቢውን ጥንቃቄ እየወሰደ ምእመናን ሚዛናዊ እንክብካቤ እንዲያገኙ ያደርጋል፣